መዝሙር 197 የጥንት አምባ ጥግ ሁነኝ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የጥንት አምባ ጥግ ሁነኝ
ከለላህ ይሰውረኝ፥
ከተወጋው ጐንህም፥
የወጣው ውኃና ደም፥
ከክፋቴ ይጠበኝ፥
ከጥፋትም ያድነኝ።
፪፡ ሕግህን መፈጸሙ
አቅቶኝ ተሸነፍሁ፥
ሌትም ቀንም አልቅሼ፥
አልጠራልኝም እድፌ፥
አንተ ብቻ መድኅኔ፥
አድነኝ ከኩነኔ።
፫፡ የምሰጥህ የለኝም
ጽድቅ አልተገኘብኝም፥
አንተ ብቻ ጽድቅ ሁነኝ፥
ጸጋህ ብቻ ያድነኝ፥
ቅዱስ ደምህ አምላኬ፥
ይሁንልኝ ሕይወቴ።
፬፡ የፍርድ ዕለትም ሲደርስ
ምድራችንም ሲፈርስ፥
ዓለም ካይንህ ፊት ሲቀልጥ፥
በግርማህ ስትገለጥ፥
የጥንት አምባ ጥግ ሁነኝ፥
ከለላህ ይሰውረኝ።