መዝሙር 170 አምባችን አምላካችን ነው የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምባችን አምላካችን ነው
እርሱም ዕቃ ጦራችን።
ከመከራችን እርሱ ነው
ጽኑ መጠጊያችን።
ያለም ገዥ ወርዶአል
ቍጣውም በዝቶአል።
በተንኮልና ኃይል
ይጣጣርብናል፤
እኛ ግን አንፈራውም።
፪፡ ኃይላችንስ አይበቃንም
ቶሎ እንጠፋለን።
ግን ያ ረድኤት እስካለነ፥
በምንም አንሸበር።
የሱስ ነው የረጁ ስም፥
ሰው ነው አምላክም።
የድል ልብስ ለብሶአል
ዙፋኑ ጸንቶአል፤
በኃይሉ ለዘላለም።
፫፡ ዓለም በጨለማ ሥልጣን
ቢገዛም ተስፋ አለን።
በአምላክ ኃይልና ብርሃን።
ሠርክ እናሸንፋለን።
ያለም ገዥ ወደቀ
ኃይሉም አለቀ።
እርሱ በአንዳችም
ሊጐዳን አይችልም፥
ከጌታ ቃል ይሸሻል።
፬፡ የአምላክ ቃል አይፋለስም
ተስፋውም ዘወትር አለን።
ለአምላክ ስንጋደልም
በእርሱ ደስ ይበለን።
ሁሉም ሲጠፋብነ፥
ቃሉ ስላነ፥
ያምላክ ፈቃድ ይሁን፥
እኛ ግን መንግሥቱን
ለርስት እንወርሳለን።