Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 114 ኢየሱስ ይመጣል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ኢየሱስ ይመጣል
በመላእክት ታጅቦ
በደሙ የዋጀውን
ለመውሰድ ሰብስቦ።
ያለ እንቅልፍ በትጋት
ነቅተው ለጠበቁት
ይመጣል ኢየሱስ
ዋጋቸውን ለመስጠት።
ትንቢት ተፈጸመ
መምጣቱ ነው ጌታ
ድልን እንድናገኝ
ሁላችን እንበርታ።
ትንቢት ተፈጸመ
መምጣቱ ነው ጌታ
ድልን እንድናገኝ
ሁላችን እንበርታ።
፪፡ እንደ ሄደ አይቀርም
ጌታችን ይመጣል
ዘመኑ አጭር ነው
ሁሉም ተፈጽሟል።
ጊዜው ሲፋጠን
እንዲህ እያየን
መንቃት ያስፈልጋል
ሲኦል እንዳይውጠን።
ትንቢት . . .።
፫፡ መምጣቴ ነው ብሎ
አዋጅ ያስነግራል
ይኸው የምሥራች
ዞትር ይሰበካል።
ድምፁን እየሰሙ
ለተከተሉት
ሲመጣ ይሰጣል
የዘላለም ሕይወት።
ትንቢት . . .።
፬፡ በጣም ተደሰቱ
በደሙ የነፃችሁ
መምጣቴ ነው ይላል
የሱስ ሊወስዳችሁ።
ስማችን የተጻፈ
በሕይወት መዝገብ
ጊዜው ተዳርሶአል
ልንሰበሰብ።
ትንቢት . . .።