Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 201 ከዓለም ዝና ክብርን ከማተርፍ የዘፈን ግጥሞች
ከዓለም ዝና ክብርን ከማተርፍ፥
መስቀል ልሸከም ስላንተ ልነቀፍ።
ስለ ቅዱስ ስምህ ብጣል ብወቀስ፥
ይፈስልኛል የክብር መንፈስ።
፩፡ ለጊዜው በኃጢአት ከማገኝ ደስታ፥
ለስምህ ልሰደድ በምድር ልንገላታ።
ዓለም በግዛትዋ ዛሬ ብትንቀኝ፥
የተገለጥክ ዕለት እቆማለሁ በቀኝ።
ከዓለም . . .።
፪፡ ጸጋህ ያስችለኛል ቢመጣ መከራ፥
አንተን አግኝቻለሁ የሕይወት
እንጀራ።
ራቁትህን ስለኔ ተሰቅለህ ሞተሃል፤
በወንጌል አላፍርም ነፍሴን
አድነሃል።
ከዓለም . . .።
፫፡ ዕድል ፈንታዬ ነህ
ኢየሱስ ሕይወቴ፥
በደምህ ታጥቤ ነፃሁ ከኃጢአቴ።
እንደ ዓለም ጥራጊ ሁኜ እንደ ጉድፍ
ብወድቅ እነሣለሁ ስላንተ ልነቀፍ።
ከዓለም . . .።